አባገዳ ኩራጃርሶ ኩራ 71ኛው የቦረና አባገዳ በመሆን ባሊ ወይንም ስልጣን ተረከቡ፡፡አባገዳ ኩራጃርሶ ኩራ የህብረተሰቡን ሰላም በማስጠበቅ የፍትህ፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን አሬሮ ወረዳ እየተካሄደ የሚገኘው 71ኛው የቦረና አባገዳ የሥልጣን ርክክብ ስነ-ስርዓት እንደቀጠለ ነው፡፡